የከተማ መሬት መረጃ አያያዝን ማዘመን በመጀመሩ፡ ባለጉዳዮች ፈጣን አገልግሎት ማግኘት ችለዋል”

አቶ ድንበሩ ተስፉ

የከተማ መሬት መረጃ አያያዝን ማዘመን በመጀመሩ፡ ባለጉዳዮች ፈጣን አገልግሎት ማግኘት ችለዋል”

አቶ ድንበሩ ተስፉ

የቢሮው መሬት ልማትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር

በ2017 በጀት ዓመት የከተማ መሬት መረጃ አያያዝን ማዘመን በመጀመሩ፡ ከ170 ሺ በላይ ባለጉዳዮች ፈጣን አገልግሎት ማግኘት የቻሉ ሲሆን፡ በተለይም ወልድያ፣ ደሴ፣ ባህርዳር፣ ደብረ ብርሃን፣ እንጅባራ፣ ጎንደር፣ ቻግኒ፣ አዘና፣ አጋው ግምጃቤት፣ ቅላጅ፣ ቅዳማጃና ዳንግላ ከተሞች መረጃን በማዘመን የተሻለ ደረጃ ያላቸው መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

በክልሉ ከተሞች ለተለያየ ልማት የሚውል 6779 ሄ/ር መሬት በማዘጋጀትና 1768 ሄ/ር በማስተላለፍ ውጤታማ ስራ መሰራቱን የገለጹት ዳይሬክተሩ፡ ጠንካራ የልማት ክትትል ስርዓት በመዘርጋት ለረጅም ዓመታት ታጥረው የተያዙ 664 ቦታዎች ላይ 126 ሄ/ር በመንጠቅ ወደ መሬት ባንክ በማስገባት በኩል ባህር ዳር እና ጎንደር ከተሞች የተሻሉ ናቸው ብለዋል፡፡

በከተሞች ለመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ለማግኘት ለተደራጁ የህብረት ስራ ማህበራት ቦታ 586.4 ሄ/ር መሬት በማዘጋጀት ለ21ሺ 312 ማኅበር አባላት ማስተላለፍ መቻሉን የገለጹት ዳይሬክተሩ ወደ ሊዝ ያልገቡ 97 ከተሞችን ወደ ሊዝ ስርዓት እንዲገቡ መደረጉን ገልጸዋል፡፡

አቶ ድንበሩ አክለውም በቀጣይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በሁሉም ከተሞች የተጀመረውን የአሰራር ስርዓት ወጥነት ባለው መንገድ በመዘርጋት ብልሹ አሰራርን መከላከልና የዘርፉን አደረጃጀት በማስተካከል ፈጣንና ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት የልማት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡፡

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top