“ተማሪዎች እንዲመዘገቡ የተጀመረው ንቅናቄ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት” መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር)

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

Facebook

ANRS Bureau of Urban and Infrastructure

dteopsroSn1i:1iu22Att5 u8gf449016s 50tg42tal0u5u 9g4c9a151ua ·

“ተማሪዎች እንዲመዘገቡ የተጀመረው ንቅናቄ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት” መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር)

ባሕር ዳር: ነሐሴ 23/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኀላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር) በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን የትምህርት ምዝገባ አስመልክተው ከሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሽን ባለሙያዎች እና መሪዎች ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱ የሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሽን መዋቅሩ ተማሪዎች እንዲመዘገቡ እያደረጉት ያለው አስተዋጽኦ የሚደነቅ መኾኑን አንስተዋል።

ቢሮ ኀላፊው ሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሽን በትኩረት ሲሠራ ብዙ ጉዳዮችን ይቀይራል፤ ቀይሯልም ነው ያሉት። የትምህርት ጉዳይ ልዩ አጀንዳ መኾኑንም ተናግረዋል። በተሠራው ሥራ ውጤት ተመዝግቧል ነው ያሉት። ትምህርት ላይ የተቃጣ ጥቃት ትውልድን እንደሚጎዳም ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ሕዝብ በትምህርት ላይ የደረሰው ስብራት እንዲጠገን እና ልጆቹ እንዲማሩለት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለውም ገልጸዋል።

የትምህርት ሥራ የሁሉንም ድጋፍ ይፈልጋል ያሉት ኀላፊው የአማራ ክልል በትምህርት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት ቆይቷል፤ ከጉዳቱ እንዲያገግምም በጋራ መሥራት ይገባል ነው ያሉት። ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ ውጭ ማድረግ ትውልድን ማምከን ነው፣ ይህን በመረዳት መሥራት ይገባል ብለዋል።

ትምህርት የሕልውና ጉዳይ ነው፤ ለሕልውና ደግሞ በትኩረት መሥራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት። አያሌ ምሁራን የሚወጡበት ክልል ተወዳዳሪ እንዳይሆን እየተደረገ ነው፣ ይህ ደግሞ ሕዝብን በዘላቂነት የሚጎዳ ነው ብለዋል። ትምህርትን መጉዳት የጠላትን አጀንዳ ማስፈጸም እንደኾነም አንስተዋል።

የሚዲያ እና የኮሙዩኒኬሽን ዘርፉ ሀገር የሚለውጥ እና ትውልድን የሚታደግ ሥራ መሥራት እንደሚገባውም ገልጸዋል። በክልሉ ያለው ምዝገባ ተስፋ የሚሰጥ እና የተሻለ ነው ያሉት ኀላፊው ነገር ግን አሁንም ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ እንዲመዘገቡ ይፈለጋል ነው ያሉት። በተማሪዎች ምዝገባ ወደኋላ የቀሩትን አካባቢዎች በመደገፍ እንዲያስመዘግቡ ማድረግ ይገባል ብለዋል። ከዚህ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ እንዲኾኑ መፍቀድ እንደማይገባም አሳስበዋል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top