ፕሮጀክቱ በከተሞች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ኑሮ እያሻሻለ ነው – ሚኒስቴሩ

ፕፕሮጀክቱ በከተሞች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ኑሮ እያሻሻለ ነው – ሚኒስቴሩ

አዳማ፤ ሐምሌ 28/2017(ኢዜአ)፡- በሀገሪቱ ተግባራዊ የሆነው የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔትና የሥራ ፕሮጀክት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ኑሮ እያሻሻለ መሆኑን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ በፕሮጀክቱ የ2017 በጀት ዓመት ማጠቃለያ እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ ውይይት በአዳማ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

በዚህ ወቅት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ መንግስት ከአለም ባንክ ጋር በመቀናጀት በተመረጡ የሀገሪቱ ከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔትና የሥራ ፕሮጀክት ተግባራዊ እያደረገ ነው።

ፕሮጀክቱ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ የከተሞችን ጽዳት፣ ውበትና የአነስተኛ መሰረተ ልማት ችግሮችን የሚያቃልል መሆኑን ጠቁመው፤ መንግስት በትኩረት ከሚያስፈጽማቸው ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት በፕሮጀክቱ በርካታ ዜጎችን ከተረጂነት በመላቀቅ አምራች ዜጋ ማፍራት ማስቻሉን አመልክተው፤ በፕሮጀክቱ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ኑሮ በማሻሻል በኩል ውጤት እየተመዘገበበት መሆኑን ተናግረዋል።

ከአለም ባንክ እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በተለያየ ጊዜ ያደረግናቸው የሥራ አፈጻጸም ግምገማዎች የሚያመለክቱት ፕሮጀክቱ ከመነሻው ካስቀመጠው ግብ አንጻር አበረታች ውጤት የታየበት ነውም ብለዋል።

ፕሮጀክቱ ውጤታማ መሆኑን ተከትሎ ከተጠናቀቀው በጀት ዓመት ጀምሮ ለተከታታይ ሦስት ዓመታት ተግባራዊ የሚሆን 45 ቢሊዮን ብር በጀት እንደተመደበለት ገልጸዋል።

ይህም ላለፉት ዓመታት በፕሮጀክቱ የተለያዩ ድጋፎች ሲደረግላቸው ዜጎች በዘላቂነት ኑሯቸው እንዲሻሻልና ከራሳቸው አልፈው በሀገር ኢኮኖሚ ላይ አስተዋጽኦ እንዲኖራቸው ያግዛል ብለዋል።

በሚኒስቴሩ የከተሞች ምግብ ዋስትናና ሴፍቲኔት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ብርሃኑ ተሾመ በበኩላቸው፤ በ11 ከተሞች የተጀመረው የከተሞች ሴፍቲኔት መርሃ ግብር አሁን ላይ በ88 ከተሞች ተግባራዊ መደረጉን ገልጸዋል።

በዚህም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ህይወት ለመቀየር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል።

የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት የስራና የቁጠባ ባህላቸውን ከማሳደግ በተጨማሪ የገቢ ማስገኛ መስክ ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ በዚህ ዓመት ብቻ 288ሺህ በላይ ዜጎችን በማስመረቅ ለውጤት ማብቃት መቻሉን አስረድተዋል።

ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የአማራ ክልል የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት አስተባባሪ ሀሰን ሙህዬ ፕሮጀክቱ በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ኑሮ ከማሻሻል በተጓዳኝ ከተሞች ውብ፣ ጽዱና አረንጓዴ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በተለይ በፕሮጀክቱ በታቀፉ 18 ከተሞች ውስጥ በተደረገው እንቅስቃሴ የስራና የቁጠባ ባህል በማሻሻልና በከተማ ግብርና ሥራ በማሰማራት በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የኦሮሚያ ክልል የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት አስተባባሪ ደበሎ ዱሬሳ በበኩላቸው፤ በፕሮጀክቱ አማካኝነት በርካታ ዜጎች በአካባቢ ልማት፤ በቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛሉ ብለዋል።

በፕሮጀክቱ በዚህ ዓመት ብቻ 61ሺህ ተጠቃሚዎች ጥሪት አፍርተው ከተረጂነት ወደ አምራችነት መሸጋገራቸውን አስረድተዋል።

ለስድስት ቀናት በተዘጋጀው በዚሁ መድረክ ላይ ከሁሉም ክልሎችሮጀክቱ በከተሞች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ኑሮ እያሻሻለ ነው – ሚኒስቴሩ

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top