የቢሮዉ መልዕክት
የምንመራው የአብክመ ከተሞችና መሰረተ-ልማ ቢሮም በከተሞች ጉዳይ ላይ ቁልፍ ሚና ያለውና ከተሞች የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ለውጥ ሞተርና ማዕከል፣ ውብና ጽዱ፣ ለኑሮ ተስማሚ እንዲሆኑ በማስቻል ለክልላችን ብሎም ለአገራችን ብልፅግና ወሳኝ የሆኑ ተግባራት የሚከናወኑበት ነው፡፡ በመሆኑም ቢሮው የክልሉ ከተሞች ዘመናዊ የመሬት አስተዳደር ስርዓት የተከተሉ፣ በፕላን የሚመሩ፣ መሰረተ ልማት የተስፋፋባቸው፣ ውብና ፅዱ፣ የልማትና የአገልግሎት ማዕከል እንዲሆኑ በማስቻልና የዳበረ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ በመገንባት የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥን እንደ ተልዕኮ ይዞ ባለፉት ዓመታት ባከናወናቸው ተግባራት በርካታ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በክልላችን በየአካባቢው አዳዲስ ከተሞች መፈጠር፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ
ፍልሰት እና የነባር ከተሞች ወደ ጎን መስፋት ከተፈጥሮዓዊው የህዝብ ዕድገት ጋር ተዳምሮ የከተሞች ህዝብ ብዛት ከሚጠበቀው በላይ በፍጥነት የጨመረበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ይህን ተከትሎም በከተሞች የአገልግሎት አሰጣጡ ተደራሽ እና አርኪ ያልሆነበት፣ ሌብነት በስፋት የሚስተዋልበት፣ የፕላን ጥሰትና ህገ-ወጥ የመሬት ወረራ የተበራከተበት፣ የመኖሪያ ቤት እና የመሰረተ ልማት ፋላጎት በእጅጉ የጨመረበት እንዲሁም ሥራ አጥነት እና የከተማ ድህነት የተስፋፋበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ በተለይም በከተሞች የሚታየውን ሌብነት መታገል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት ልዩ ትኩረት የሚሻው ጉዳይ ነው፡፡

አሕመዲን መሐመድ (ዶ.ር)
በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ክላስተር ዘርፍ አሥተባባሪ እና የአብክመ ከተሞችና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ
የተመረጡ አገልግሎቶች
አዳዲስ ዜናዎች
- 1
- 2
የቢሮው አስተዳደሮች

አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር)
በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ክላስተር ዘርፍ አሥተባባሪ እና የአብክመ ከተሞችና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ

አቶ ሱለይማን እሸቱ
ምክትል ቢሮ ኃላፊ

አቶ አሰፋ ሲሳይ
ምክትል ቢሮ ኃላፊ

አቶ አላምር ተሻለ
የከተሞችና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ

አቶ ሺቤ ክንዴ
የቢሮ አማካሪ

አዲሱ ደባልቄ (ዶ/ር)
በምክትል ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
በክልላችን የሚገኙ ከተሞች
በክልሉ ከሚገኙ 60,560 የመንግስት ቤቶች ውስጥ ቤቶች ወደ ዘመናዊ የመረጃ ቋት (ሶፍትዌር) የገቡ
በዘርፉ በሚከናወኑ የልማት ስራዎች ላይ ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል የተፈጠረላቸዉ
